7.

በእግዝአብሔር ኃይል ውስጥ መኖር

ክለሳ
  1. ባለፈው ሳምንት እንድታመሰግን ያደረጉ ምን ምን ነበሩ?
  2. ያስቸገረህ/ሽ ነገር አለ? እንዴት እንርዳህ/ሽ?
  3. ለህብረተሰባችን/ለግቢያችን/ለትምህርት ቤታችን ያስፈልጋሉ ብለህ/ሽ የምታስበው/ቢው ነገር አለ?

በሚያስፈልጉት ነገሮች ሁሉ ላይ ለርስ በርሳችን መፀለይ አስፈላጊ ነው::

  1. የባለፈው ሳምንት ጥናታችን እንዴት አተገበርከው?
  2. ታርኩን ለማን አካፈልከው? ምላሻቸውስ ምን ነበር?
ትኩረት

ቁልፍ ጥያቄ:  በጣም አስቸጋሪ በሆነው ሁኔታ ውስጥ የክርስትናን ህይወት እንዴት መኖር እንችላለን?

መግለጫ:  በራሳችን ብርታት እግዝአብሔር የምፈልገውን ህይወት መኖር አንችልም:: በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ግን እግዝአብሔር የምፈልገውን ህይወት ለመኖር ኃይል እናገኛለን::

በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ለህይወትህ ትርጉም ያለው ነገር አለ?

  1. ለመረዳት የከበደህ/ሽ ነገር ነበር?
  2. የዛሬ ጽሑፍ ስለ እግዝአብሔር ምን ይነግረናል? ስለ ሰዎችስ? በእግዝአብሔር እና በእኛ መካከል ስላለው ግንኙነትስ?
  3. ይህ ጽሑፍ ከላይ ያነሳነው ጥያቄዎች ጋር ይገናኛል ብለህ/ሽ ታስባለህ/ሽ?  "እንዴት የክርስትና ሕይወት መኖር ነው?"
  4. በዚህ ጽሑፍ ላይ ጥያቄ ወይም አስትያየት አለህ/ሽ?
  5. ዛሬ የተማርነውን ነገር እንዴት ታጠቃልላለህ/ሽ?

ማጠቃለያ:

 

በመንፈስ ቅዱስ በሚሰጠን ኃይል እግዝአብሔር የምፈልገውን ህይወት መኖር እና እርሱን ማስደሰት እንችላለን:: ይህንን ህይወት በራሳችን ኃይል መኖር ብንሞክር ፍሬ አናፈራም: እግዝአብሔር የምፈልገውንም ህይወት መኖር አንችልም:: ስለዚህ ሁል ግዜ በመንፈስ ቅዱስ መደገፍ: መመራትም አለብን::

ከመጀመርያ እንደተማርነው በደምብ ልረዳን የሚችል ምሳሌ መተንፈስ ነው:: ኦክስጂን (ንጽሁ አየር) ወደ ውስጥ: ካርቦንዳዮክሳይድ (የተቃጠለ አየር) ደግሞ ወደ ውጪ እንደምንተነፍስ ሁሉ የመንፈስ ህይወትም እንደዚሁ ነው:: ይህም የመንፈስ መተንፈስ ኃጣታችን ስንናዘዝ (ባለፈው ሳምንት እንደ አየነው) ወደ ውጪ እንተነፍሳለን: በመንፈስ ቅዱስ በሚሰጠን ኃይል በመደገፍ ወደ ውስጥ እንተነፍሳለን:: ሁል ግዜ ይህን ካደረግክ/ሽ እግዝአብሔር ካንተ/ቺ የሚፈልገውን ህይወት መኖር ትችላለህ/ሽ::

ትግበራ (ወደ ስራ መቀየር)

በጣም አስፈላጊ ነገር የተማርነውን ስራ ላይ ማዋልነው:: ይህን ለማድረግ ሁላችንም መረዳዳት አለብን:: እነኚ ጥያቄዎች ልረዱን ይችላሉ::

  1. ይህ እንዴት ልሆን ይችላል ወይስ በዚህ ለውጥ እንዴት ልትኖር/ሪ ትችላለህ/ሽ? ከእግዝአብሔር ከራስህ እና ከሌሎቹ ጋር እንዴት ትኖራለህ/ሽ?
  2. ከዚህ ሳምንት ውይዪት በኋላ በህይወትህ ውስጥ ምን ትሰራለህ/ሽ?
  3. በዝህ ሳምንት የተማርነውን ከማን ጋር ትካፈላለህ? ስለ ምን ትካፈላለህ/ሽ?

ለማተም ንድፍ አውርድ
firststepswithgod.com/amh/print/7