8.

ከእግዝአብሔር ጋር መነጋገር

አካፍል
  1. በዚህ ሳምንት ከእግዚአብሔር ጋራ እንዴት ሳለፍክ/ሽ?
  2. እንድታመሰግን ያደረገ ነገር ምንድር ነው?
  3. እግዝአብሔር ምን እንዲረዳህ ትፈልግሃለህ?
  4. በምያስፈልግህ ነገር ውሰጥ እንዴት ልንረዳህ እንችላለን;
  5. ለእርስበርሳቸችሁ ፀልዩ
ክለሳ
  1. ከባለፈው ስብሰባችን ወዲህ ምን ምን ተለማምደሃል?
  2. እያንከባከብካቸው ያሉተ ሰዎች እንዴት ናቸው? በጣም የሚጠቅማቸው ነገር ምነድር ነው?
  3. የእግዝአብሔርን ለሌሎች ማካፍል ትችላለህ? ከነርሱ ጋር ፀልየሃል?
  4. ለነዚያ ሰዎች ፀልይ
አንብብ
  1. ንባቡን ድምጽህን ከፍ አርግና ሁለት ግዜ አንብብ
  2. በቡድኑ እርዳታ አንድ ሰው ንባቡን በቃሉ እንዲያነብ አርጉት
  3. የተጨመረ አዲስ ነገር ወይም የጎደለ ነገር አለ?

የማቴዎስ ወንጌል 6:9-15

9 እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፦ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥

10 ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤

11 የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤

12 እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፤

13 ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን፤ መንግሥት ያንተ ናትና ኃይልም ክብርም ለዘለዓለሙ፤ አሜን።

14 ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤

15 ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።


በስፋት አንብብ

አጣራ
  1. ይህ ንባብ ላንተ ምን ጥቅም አለው?
  2. ከዚህ ንባብ የወደድከው ነገር ወይ የረበሸ ነገር አለ?
  3. የህ ንባብ ስለ ሰው እና ስለ እግዝአብሔር ምን ይነግርሃል?
አተግብር
  1. የህን ንባብ መሰረት በማድረግ ታደርግ ዘንድ እግዝአብሔር ካንተ የሚፈልገውን ነገር ጠይቅ፤ ምን ምን ናቸው?
    • መቀየር ያለበት ፀባይ
    • መጠየቅ ያለበት ቃል ክዳን
    • መከተል የሚገባው ምሳሌ
    • መጠበቅ ያለበት ትዕዛዝ
  2. ይህን ለቡድኑ አካፍል
ማስታወሻ

ምንም እንኳን የኢየሱስ ሞት እና ትንሳዔ ለሁሉም ሰው ኃጥአት ዋጋ የተከፈለ ብሆንም፣ ኃጥአት ባንዴ ወይ በቅዝበት ይቅር ይባላል ማለት አይደለም፡፡ኢየሱስ ዛሬ ይቅርታን ወይ ምህረትን እንድንቀበል የሚያስችለን አጋጣሚ ፈጠረልን፡፡

ኃጥአታችን እንዲሰረይልን ሁለት ነገር ማድረግ አለብን፡

  1. እግዝአብሔርን ይቅርታ መጠየቅ
  2. ለሌሎች ሰዎች ይቅርታ ማድረግ

እግዝአብሔር ይቅር ስለን ኢየሱስ ስለሞተልን ኃጥአታችን ድጋሜ አይቆጥርብንም፡፡ እርሱ ልንቀጣበት የነበረውን የኃጥአታችንን ዋጋ ተቀበለ፤ እኛም ነጻ ወጣን፡፡ በዚህ እውነት መሰረት፣ እኛ በደለኞች ሆነን ሳለን እግዝአብሔር መልሰው በበደላችን አይቀጣንም፡፡ አመጸኞች ሆነን ሳለን ቅዱሰን አደረግን፡፡ ይህ ከእግዝአብሔር ጋር ለመታረቅ መሰረት ነው፡፡ ምንኛ መታደል ነው!

እኛ ለበደሉን ሰዎች ይቅርታ ስናደርግላቸው የተደረገውን ነገር እንረሰዋለን ወይም እንክዳለን ወይም እንደመስሳለን ማለት አይደለም፡፡ በዚህ አውድ፣ “ይቅርታ ማድረግ” ማለት ማተው ነው፡፡ ሁሉንም ነገር ለእግዝአብሔር አሳልፈን መስጠት አለብን፡፡ እንድን ሰው ይቅር ስንል፣ ሁሉንም ነገር ለእግዝአብሔር ትተን ማለት ነው፣ ከሰውዬው ጋር ያለን ሕብረት ከኃጥአት ሸክም ነጻ ይሆናል፡፡ በጭራሽ ቂም መያዝ ወ ይ መበቀል ማሰብ የለብንም፡፡ ከዚህ ይልቅ ከሸክም ነጻ ወጥተን ከርሱ ጋር እንግባባለን፤ በደል ከዚህ በኋላ በመካከላችን አይኖረናል፡፡