5.

አዲስ ክዳን

አካፍል
  1. በዚህ ሳምንት ከእግዚአብሔር ጋራ እንዴት ሳለፍክ/ሽ?
  2. እንድታመሰግን ያደረገ ነገር ምንድር ነው?
  3. እግዝአብሔር ምን እንዲረዳህ ትፈልግሃለህ?
  4. በምያስፈልግህ ነገር ውሰጥ እንዴት ልንረዳህ እንችላለን;
  5. ለእርስበርሳቸችሁ ፀልዩ
ክለሳ
  1. ከባለፈው ስብሰባችን ወዲህ ምን ምን ተለማምደሃል?
  2. እያንከባከብካቸው ያሉተ ሰዎች እንዴት ናቸው? በጣም የሚጠቅማቸው ነገር ምነድር ነው?
  3. የእግዝአብሔርን ለሌሎች ማካፍል ትችላለህ? ከነርሱ ጋር ፀልየሃል?
  4. ለነዚያ ሰዎች ፀልይ
አንብብ
  1. ንባቡን ድምጽህን ከፍ አርግና ሁለት ግዜ አንብብ
  2. በቡድኑ እርዳታ አንድ ሰው ንባቡን በቃሉ እንዲያነብ አርጉት
  3. የተጨመረ አዲስ ነገር ወይም የጎደለ ነገር አለ?

ትንቢተ ኤርምያስ 31:31-34

31 እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፤

32 ከግብጽ አገር አወጣቸው ዘንድ እጃቸውን በያዝሁበት ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንደ ገባሁት ያለ ቃል ኪዳን አይደለም፤ እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና፥ እኔም ቸል አልኋቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡

33 ከእነዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፥ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል።

34 እያንዳንዱ ሰው ባልንጀራውን፥ እያንዳንዱም ወንድሙን፦ እግዚአብሔርን እወቅ ብሎ አያስተምርም፤ ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ያውቁኛልና፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ በደላቸውን እምራቸዋለሁና፥ ኃጢአታቸውንም ከእንግዲህ ወዲህ አላስብምና።


በስፋት አንብብ

ትንቢተ ኢሳይያስ 59:1-2

1 እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ከማዳን አላጠረችም፥ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም፤

2 ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች፥ እንዳይሰማም ኃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል።


በስፋት አንብብ

አጣራ
  1. ይህ ንባብ ላንተ ምን ጥቅም አለው?
  2. ከዚህ ንባብ የወደድከው ነገር ወይ የረበሸ ነገር አለ?
  3. የህ ንባብ ስለ ሰው እና ስለ እግዝአብሔር ምን ይነግርሃል?
አተግብር
  1. የህን ንባብ መሰረት በማድረግ ታደርግ ዘንድ እግዝአብሔር ካንተ የሚፈልገውን ነገር ጠይቅ፤ ምን ምን ናቸው?
    • መቀየር ያለበት ፀባይ
    • መጠየቅ ያለበት ቃል ክዳን
    • መከተል የሚገባው ምሳሌ
    • መጠበቅ ያለበት ትዕዛዝ
  2. ይህን ለቡድኑ አካፍል
ማስታወሻ

ታማኝ እንሁን፡፡ አስርቱን ትዕዛዛት በትክክል እየጠበቅክ ነው ወይስ በተከታታይ እየጣስካቸው መሆኑ ተሰምቶሃል? እነኚህ ሕጎች ክፋትን ለመከላከል ብጠቅሙም፣ ጨርሰው ልደመስሱ አይችሉም፡፡ እኛ ሰዎች ክፋት ነጻ መሆን እራሳችንም መቀየርም የማንችል መሆኑ የማይቀየር እውነት፡፡

ለዚህ ነበር እግዝአብሔር ልመጣ ስላለው የአዲስ የህይወት መንገድ ዘመን የተናገር ነው፡፡ ይህ ልሆን ዘንድ መቀየር ያለበት ነገሮች አሉ፡

  1. እኛ ሰዎች እግዝአብሔር ላይ ተነስተን እባቡን በተከተልን ግዜ ገነት መልቀቃችን ግድ ሆነብን፤ ከእግዝአብሔር ጋር ያለን ሕብረታችንም ተቋረጠ፡፡ በእግዝአብሔር ላይ ኃጥአትን ሰርተናል፤ ወደ ኋላ መመለስም አንችልም፡፡ ግን እግዝአብሔር በጣም ስለ ወደደን ለኃጥአታችን ይቅርታ እንደሚያደርግልን አሳወቀን፡፡ ይህ የመጀመሪያ ሰዎች ከእግዝአብሔር የነበራቸውን ሕብረት ድጋሜ እንድናገኝ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
  2. በክፋት ተፅዕኖ ስር ድጋሜ እንዳንገባ እንዲሁም በእግዝአብሔር እና በእባቡ (ክፉውን) ምርጫ እንዳንሄድ እግዝአብሔር ልባችን መቀየር ይፈልጋል፡፡ እግዝአብሔርን መልካምነትንም ብንመጥ የእግዝአብሔር ሕግ ተመልሰው በኛ ላይ ይፈጸማል፤ እባቡን ከመረጥን ግን ተመልሰን በክፋት ባሪያ እንሆናለን፡፡ ነገር ግን ይህን ለመወሰን መጀመሪያ እግዝአብሔርን ማወቅ ይኖርብናል፡፡ ስለዚህ እግዝአብሔር ሁሉም ሰው በግሉ እርሱን የሚያውቅበት ግዜ እንደምመጣ ተናገረ፡፡ ከእግዝአብሔር ጋር እንደዚህ ያለ ሕብረት ከኖረን፣ መጽሓፍ ላይ የተጻፉት ሕግ የምንጠብቅ ሳይሆን፣ እግዝአብሔር ሕጉን ቀጥታ ብልባችን ውስጥ ስለምጽፍ አካላችን ይሆናል፡፡
  3. ያኔ እኛ ሕዝቡ እንሆናለን፤ እርሱም አምላካችን ይሆናል፤ ብዙ ነገሮችም እግዝአብሔር በመጀመሪያ እንዳዘጋጀልን ይሆኑልናል፡፡